input
stringlengths 1
130k
⌀ |
---|
ከተለያዩ የነዳጅ ዘይት አቅራቢዎች የመጣው ሁሉ በአንድ የምርት አይነት ሊቀላቀል ይችላል። |
እንደ ፐብሊክ አይ ዘገባ ከሆነ የስዊዘርላንዶቹ ኩባንያዎች በመቀላቀሉ ብቻ ሳይሆን በነዳጅ ዘይት ማመላለሻዎች አከፋፋዮች እና ማከማቻዎች ውስጥም ባለድርሻ ናቸው። |
እነዚህ ኩባንያዎች በአፍሪቃውያን ላይ የከፋ የጤና እክል ስለሚያስከትለው የነዳጅ ዘይት የሚያወሳው ዘገባ ይፋ ሲሆን ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አይደሉም። |
በዚህ በስዊዘርላንድ ይህ ጎጂ የነዳጅ ዘይት ግብይት እንዲቆም የሚጠይቅ በ ሰዎች የተሰበሰበ ፊርማ አቅርበን ነበር። |
የተሰበሰበውን ፊርማ በዚህ በጄኔቫ ትራፊጉራ ለተባለው ኩባንያ ስናቀርብ ምንም የለወጠ ነገር የለም። |
ጥራቱ የተጓደለ የነዳጅ ዘይት የሚሸምቱት የምዕራብ አፍሪቃ ሃገራት ከፍተኛ የተፈጥሮ ዘይት ሐብት ክምችት ቢኖራቸውም ለማምረት አቅማቸው አይፈቅድም። |
ኦሊቨር ክላሰን እንደሚሉት እጅ ያጠራቸው ሃገራት ርካሽ ግን ደግሞ ለጤና አስጊ የሆነውን የነዳጅ ዘይት ለመሸመት ተገደዋል። |
ዘገባው ይፋ ከሆነ በኋላ የምዕራብ አፍሪቃ ሃገራት መንግሥታት የነዳጅ ዘይት ግብይታቸውን ከመሠረቱ ለመቀየር ቃል ገብተው ነበር። |
ጋና እና ናይጄሪያ ቃላቸውን ጠብቀው ለሚሸምቱት የነዳጅ ዘይት የነበራቸውን የጥራት መሥፈርት አሻሽለዋል። |
ነገር ግን በምዕራብ አፍሪቃ መንግሥታት እና ባለስልጣናት ዘንድ በተወሰነ ደረጃ የችግሩን አሳሳቢነት እንዲገነዘቡ አድርጓል። |
ለከባቢ አየር ብክለት ያለውን አስተዋፅዖ እና የሚያስከትለውን የጤና እክል ሁሉም እንዲነጋገርበት አድርጓል። |
የችግሩ ምንጭ እነዚህ ኩባንያዎች በአውሮጳ የማያደርጉትን በዚያ መሸጣቸው ነው። |
መንግሥታቱ ለችግሩ በፍጥነት እልባት እንሰጠዋለን ሲሉ ለሕዝባቸው ተናግረው ነበር። |
የጥራት መስፈርታቸውን ለማሻሻል እና ከአውሮጳ ጋር ለማስተካከል ፍላጎት እንዳላቸውም አሳይተዋል። |
በተለይ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በጉዳዩ እጅግ ተቆጥተው ተከታታይ ክርክሮች እና ውይይቶች ተደርገዋል። |
በአፍሪቃ መንግሥታት ላይ ከፍ ያለ ጫና የተፈጠረ ሲሆን ጋና እና ናይጄሪያ ለሚገዙት የነዳጅ ዘይት የጥራት መስፈርቱን በማስተካከል ቀዳሚ ሆነዋል። |
ድርጅታችን ካሳካቸው ትልቅ ጉዳዮች ምን አልባትም ትልቁ ይኸ ነው። |
አፍሪቃ ከአውሮጳ ከምትሸምተው የነዳጅ ዘይት በመቶው የሚያልፈው በአንትዎርፕ ሮተርዳም እና አምስተርዳም ወደቦች በኩል ነው። |
ፐብሊክ አይ የተባለው ድርጅት እነዚህ ወደቦች የአውሮጳ የጥራት መሥፈርት የማያሟላውን የነዳጅ ዘይት ወደ አፍሪቃ ከማሻገር እንዲያግዱ ጥሪ አቅርቧል። |
ኦሊቨር ክላሰን በሆላንድ እና ቤልጅየም የሚደረገው ክርክር በኩባንያዎቹ ላይ ጫና ያድራል የሚል ተስፋ አላቸው። |
የአፍሪቃ የጥራት ደረጃ የሚባለውን በሚያመርቱት በሆላንድ እና በቤልጅየም ሰፊ ሕዝባዊ ውይይት እየተደረገ ነው። |
ይኸ የጥራት ደረጃ በገበያው ቆሻሻ ነዳጅ ዘይት ተብሎ ይታወቃል። |
እናም የስዊዘርላንድ የሸቀጥ ነጋዴ ኩባንያዎች ላይ ጫና የሚያሳድር ለውጥ ይኖራል ብለን ተስፋ እናደርጋለን። |
የጋናው ምክትል ፕሬዝዳንት ማሐሙዱ ባዉሚያ አገራቸው ገቢራዊ ያደረገችው አዲሱ የጥራት መሥፈርት ከምዕባውያኑ አሊያም ከምሥራቅ አፍሪቃ ሃገራት ጎራ እንደሚያሰልፋት ተናግረዋል። |
ምክትል ፕሬዝዳንቱ የሰረሰር ሕመሞች እና ከፍተኛ ድኝ ሰልፈር ካለው የነዳጅ ዘይት የሚፈጠሩ የጤና እክሎችም ይቀንሳሉ ብለው ተስፋ አድርገዋል። |
ናይጄሪያ ከውጭ የምትሸምተው ብቻ ሳይሆን በአገር ውስጥ የሚመረተው ጭምር አዲሱን የጥራት መስፈርት ማሟላት አለበት ብላለች። |
በዚህም መሰረት ቻይና የኢንቴርኔት ነፃነት የለባቸውም በተባሉ ሀገራት ተርታ ተኛ ደረጃ የተሰጣት ስሆን ኢትዮጵያና ሶርያ ደግሞ ተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። |
ይህም የኢንተርኔት አገልግሎትን ማገድ መልዕክቶች በኢንቴርኔት እንዳይሰራጩ መከልከል በዚህ ሂደትም የተጠቃሚዎቹን መብት መጣስ በአስደንጋጭ ሁኔታ መባባሱን የሚያሳይ መሆኑንን ድርጅቱ አስታውቋል። |
የለንደኑ ቻታም ሃዉስ የተባለው የፖለቲካ ጥናት ተቋም የአፍሪቃ ፕሮግራም ተባባሪ ተመራማሪ ጀሳን ሞስል በኢትዮጵያ ዉስጥ ቴሌኮሙኒኬሼን ሴክቴሩ ነፃ አልሆንም። |
በአጠቃላይ አሁንም መንግስት በኤኮኖሚ ትልቅ ሚና ኢየተጫወተ ይገኛል ኢሕአዴግም ዘርፉ ከመንግስት እጅ እንዳይወጣ ወስኗል። |
መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት የተሌኮሙኒኬሼን መሰረተ ልማት ግንባታ ላይ ተሰማርተዋል ግን የግል የተሌኮሙኒኬሼን አገልግሎት ሰጭዎች የሉም። |
ይህ ማለት ደግሞ ከሌሎች አጋሮች የበለጠ በኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉ የኢንቴርኔት ግኑኝነቶች ከሌሎች ሀገራት ጋር ሲነፃጸር እያሽቆለቆለ እንዲሄድ አድርጓል። |
መንግስት የኢንቴርኔትን አገልግሎትን ሙሉ በሙሉ በመያዝ ገቢ ከማግኘቱም በተጨማሪ መንግስትን የሚቃወሙ ድምፆችን ለማፈንም ይጠቀምበታል ይላሉ ጀሳን። |
እንደ ጃሳን በአገሪቱ ያሉ የኢንቴርኔት በተለይ የማህበራዊ መገናኛ ብዙሀን ተጠቃሚዎች ለመንግስት ራስ ምታት ሆነውበታል። |
በጉዳዩ ላይ በዶይቼ ቬሌ የፌስቡክ ገፅ ተሳታፊዎችን አወያይተን ነበር። |
የኢንቴርኔት አጋልግሎት ዘገምተኛ በመሆኑ ገንዘባቸዉን ኢየጨረሰባቸዉ እንደሆነ ቴሌኮሙኒከሼን ሲጠየቅም መልስ እንደማይሰጥ በዋትስአፕ አስተያየት የላኩም አሉ። |
በቅርቡ ኢትዮጵያ ማህበራዊ መገናኛ ብዙሀንን የሚገድብ ረቅቅ አዋጅ እያዘጋጀች ነዉ ተብሎ ቢወራም የመንግስት ባለስልጣናት ግን አስተባብለዋል። |
ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል በፍሪደም ሃዉስ ዘገባ ላይ የበለጠ መረጃ ለማግኘት ያደረግነዉ ሙከራ አልተሳካም። |
ዓለም የባልካን ጎርፍ ያስከተለው መዘዝ በባልካን አካባቢ ሃገራት ካለፈው ቅዳሜ አንስቶ በተከሰተ የጎርፍ መጥለቅለቅ የሟቾቹ ቁጥር እየጨመረ ነው። |
አንዳንድ ድርጅቶች ተጨማሪ የውሃ ሙላት አደጋ ሊከሰት እንደሚችል እያስጠነቀቁ ነው። |
በባልካን አካባቢ በሚገኙ ሃገራት በቦስንያ ክሮሺያ እና ሰርቢያ ውስጥ የተከሰተው የጎርፍ መጥለቅለቅ እስከ አሁን ድረስ ከ የማያንሱ ሰዎችን ወስዷል። |
በተለይ ሳቫ በሚባለው ወንዝ አቅራቢያ ያለው ሰሜናዊ የቦስኒያ አካባቢ ሰብረው በወጡ ወንዞች ተጥለቅልቋል። |
ሕንፃዎች ጎርፉ ባመጣው ማጥ እና የውሃ ሙላት ተውጠው ጣሪያዎቻቸው ብቻ ነው የሚታዩት። |
የሰርቢያ ነዋሪዎች ሌላ ተጨማሪ የጎርፍ መጥለቅለቅ አደጋ ሊከሰትባቸው እንደሚችል ተተንብዮዋል። |
ጎርፉን ለመከላከል በሚልም ሳባች ሚትሮቪቻ ቤልግሬድ እና ኦብሬኖቫች በተባሉ አካባቢዎች በሚሊዮናት የሚቆጠሩ በአሸዋ የተሞሉ ከረጢቶች ተከምረዋል። |
ሰኞ ማታ ከ የኦብሬኖቫች ነዋሪዎች ያህሉ ከተማዋን እንዲለቁ ተደርገዋል። |
ሠርቢያ መዲናም ጭንቅ ውስጥ ሆና ነዋሪዎቿ ከሠዓት ጋር ሩጫ ይዘዋል። |
ከ ዓመታት ወዲህ አደገኛው በተባለለት የባልካን የጎርፍ አደጋ ከከተሞች ባሻገር የገጠር አካባቢዎችም ከፍተኛ ጉዳት እንደተከሰተባቸው ተነግሯል። |
የሠብዓዊ ርዳታ ድርጅት ውስጥ የሚያገለግሉት ፍሪትስ ኖይበርግ የባልካን ሃገራት የጎርፍ መጥለቅለቅ በጎርፉ የተነሳ ገበሬዎች በከፍተኛ ሁኔታ ተጎድተዋል። |
ዝናቡ መውረድ ከጀመረ አራት ሣምንታትን አስቆጥሯል እናም በሚቀጥሉት ሣምንታት ካላባራ ምርት የሚባል ነገር አይኖርም። |
በእዚህ ዓመት የሚበቅል ነገር ከሌለ የሕዝቡ ቀለብ ምን ሊመስል እንደሚችል መገመት ይቻላል። |
ጎርፉ አግበስብሶ ካመጣቸው የቆሻሻ ቁልሎች ባሻገር ውሃው በነዳጅ ዝቃጭ ተበክሏል። |
የውሃው መበከል እንደ ታይፎይድ እና የጉበት መመረዝ ዓይነት በሽታዎችን ሊያስከትል ይችላልም ተብሏል። |
ከእዚያ ባሻገር በሺህዎች የሚቆጠሩ ላሞች አሣሞች በጎች ውሾች እንዲሁም ሌሎች እንስሳት በመሞታቸው ወረርሺኝ ሊከሰት ይችላል ሲሉም ተንታኞች ፍራቻቸውን ገልጠዋል። |
በአካባቢው የሚገኝ ሄልፕ የተባለው የሠብዓዊ ርዳታ ድርጅት ኃላፊ የሆኑት ክላውስ ሞክ ፍራቻቸውን እንዲህ ይገልጣሉ። |
ውሃው እየቀነሰ ሲሆን በተመሳሳይ ጊዜ የዓየር ሙቀቱ እየጨመረ ነው። |
ይኽም ፈንጂዎቹ በካርታ ላይ ይገኙባቸው የነበሩ ጥቁምታዎች የተዛቡ እንዲሆኑ አድርጓል። |
ፍሪት ኖይበርግ የሰርቢያ የጎርፍ መጥለቅለቅ ከሔሊኮፕተር ሲቃኝ ይኽ ማለት የፈንጂ ቃጣና ተብለው ካርታ ላይ ምልክት የተደረገባቸው መስኮች አሁን ተዛብተዋል። |
እናም ሰዉ መንገድ ላይ ሲሄድ ፈንጂ ላይ ላለመቆም ጥንቃቄ ማድረግ አለበት። |
ከቦስኒያ የሚነሱ ወንዞች ፈንጂዎቹን ወደ ሌሎች ደቡብ አውሮጳ ሃገራት ይዘው እንዳይሄዱ አስግቷል። |
የፈንጂዎቹ ማቀጣጠያ በጎርፉ የተነሳ ርጥበት ስላጋጠማቸውም ባልተጠበቀ መልኩ ሊፈነዱ ይችሉ ይሆናል ተብሏል። |
የኃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫዎችንም በጎርፉ የተወሰዱ ፈንጂዎች እንዳይመቱ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል። |
የጎርፉ አደጋ ለተጋረጠባቸው ነዋሪዎች የርዳታ ርብርብ እየተደረገ ሲሆን የጀርመን የርዳታ ድርጅቶች የቴክኒክ እገዛ እያደረጉ እንደሚገኙ ተጠቅሷል። |
ጀርመን እስካሁን ለጉዳቱ ሰለቦች የሚውል በሚል ዩሮ ርዳታ እንደሰጠች ከውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የተገኘው መረጃ ጠቁሟል። |
ባህል ቤተ ውበት በአርጎባ በየትኛውም ባህል ውስጥ የሚኖሩ ህዝቦች ውበትን ያደንቃሉ። |
ውበት የአንድ ነገር መስህብ የሚያረካ ወይም የሚያስደስት ገጽታ ነው። |
ቤተ ውበት በአርጎባ የአርጎባ ብሄረሰብ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች ማለትም በአማራ በኦሮሚያ በአፋርና በሀረሪ ውስጥ ይኖራሉ። |
አርጎባ የሚለው የብሄረሰቡ መጠሪያ አረብ ገባ ከሚለው የመጣ መሆኑ ይነገራል። |
የአርጎባ ቋንቋ ወደ አማርኛ ቋንቋ ዘዬ ወሰድ ቢያደርገውም የተለየና ራሱን የቻለ ቋንቋ ነው። |
በአርጎባ ብሄረሰብ የአለባበስ የሰርግ የሀዘን ስርአቱ ሌሎችም ማንነቱን መግለጫ የሆኑ ባህሎች አሉ። |
ጭስ የአርጎባ የሴቶች ውበት መጠበቂያ መሆኑን ሁለት የብሄረሰቡ ተወላጆች አጫውተውኛል። |
የአጠቃቀሙ ሂደት ምን እንደሚመስል ወ ት ጀሚላን ጠይቂያት ነበር። |
ወይባ የራሱ የሆነ ሽታ ለመቀየር ጠረንዋ እንዲጣፍጥ አዝጋሮውን ትጠቀማለች። |
ወይባ ጭስ ከውበት ባለፈ በጤናው በኩል ፍቱን ፈውስ እንደሆነ ወ ት ጀሚላ ገልጻልኛለች። |
በወጣትነቷ ጭሱን ትታጠን ከነበረ ውበቷ ብታረጅ እንኳን ወዟ እንዳለና እንዳማረባት ምስክርነት በእይታ መስጠት ይቻላል ትለናለች ጀሚላ። |
ነገር ግን ልታገባ ያለች ሙሽራ ከሰርጓ ቀን ቀደም ብላ ወይባ ትሞቃለች። |
ውበቷ ለ ወር ምንም ሳትጠቀም ሊቆይ እንደሚችል ወ ት ጀሚላ ገልጻልኛለች። |
የአርጎባ ሴት ከውበት ማስዋቢያም ባለፈ ለባልዋ ፍላጎቷን የምትገልጽው ጭሱን በመታጠን ነው። |
ሚስት የጾታዊ ግንኙነት ፍላጎት ሲኖራት በቃላት መግለጽ አይጠበቅባትም እንደአርጎባ ብሄረሰብ። |
ወሮ ከድጃ ከ አመታቸው ጀምሮ ለተከታታይ አመታት አሁን እስካሉበት እድሜ ድረስ በሳምንት ሁለት ጊዜ የወይባ ጭስ እንደሚሞቁ ነግረውኛል። |
በአፋር ክልል የአርጎባ ልዩ ወረዳ ባህል ቱሪዝምና የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽ ቤት ሀላፊ ናቸው። |
የማንነቱ መገለጫ የሆኑ እሴቶቹን እንዳይጠፋ በመንከባከብ ከትውልድ ትውልድ እንዲተላለፍ በተለያዩ ግንዛቤ በማስጨበጫ መንገዶች ለህብረተሰቡ የማስተላለፍ ስራ እየተሰራ እንደሆነ ገልጸውልኛል። |
ባህል የማንነት መገለጫ መሆኑን አውቆ እንዲጠብቅ ከፍተኛ ጥረት እየተደረ ነው አቶ ኑርሁሴን እንዳሉት። |
የኬንያ መንግስት መንገዶቹን የዘጋዉ ከኢትዮጵያ ጋር በሚያዋስነዉ ድንበር በርካታ ሕገ ወጥ ጦር መሳሪዎች ከተያዙ በኋላ ነዉ። |
አንድ የኬንያ ባለስልጣን ግን መንገዶቹ በኢትዮጵያና በኬንያ መንግስታት ስምምነት መዘጋታቸዉን አጋልጠዋል። |
የሐዋሳዉ ወኪላችን ሸዋን ግዛዉ ወጋየሁ ያነጋገራቸዉ የሞያሌ ነዋሪዎች እንደሚሉት መንገዶቹ በመዘጋታቸዉ የትራንስፖርትና የህዝብ ዝዉዉር ተስተጓጉላል። |
መነኮሳትን ጨምሮ ክሳቸው የተቋረጠ ተጠርጣሪዎች ተፈቱ ኢትዮጵያ መነኮሳት እና የዩኒቨርሲቲ መምህራንን ጨምሮ የቀረበባቸው ክስ የተቋረጠላቸው ተጠርጣሪዎችን እየፈታች ነው። |
የአዲስ አበባ ወኪላችን ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር ሁኔታዎችን ለማየት ወደ አዋሽ ተጉዞ ነበር። |
የትግራይ ምክትል ርዕሠ መስተዳድር ያስተላለፉትን ማስጠንቀቂያ ራድዮ ለርስዎ የምናቀርበውን አገልግሎታችንን ለማሻሻል በማሰብ ኩኪዎችን እንጠቀማለን። |
በሀገሪቱ የሚካሄደው ለውጥ እንዳይሰናል ህብረተሰቡ በመጪው ዓመት መቃቃር እና ጥላቻን ከሚያስከትሉ አባባሎችም እንዲርቅም ጠይቀዋል። |
አቡነ ማትያስ ዛሬ አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ህዝቡ ከምንም በላይ ለፍቅር እና ለአንድነት ቦታ እንዲሰጥ ተማጽነዋል። |
መግለጫውን የተከታተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝሩን ልኮልናል። |
በቻርልስ ቴይለር ላይ የተላለፈው የጥፋተኝነት ብይን ለሌሎች መቀጣጫ እንደሚሆን ነው ናይጀሪያዊው ጂብሪል ኢብራሂም ከዴሞክራሲና ልማት ማዕከል ያምናሉ። |
በሥልጣን ላይ ያሉ መሪዎች በሥልጣን ላይ ባሉበት ጊዜ ለሚወስዱት ርምጃ ሁሉ በኃላፊነት ሊጠየቁ እንደሚችሉ ጠቋሚ ነው። |
ቴይለርም በሥልጣን በነበሩበት ጊዜ የመንግሥትን ንብረት ለመግደል፡ ለማጥፋት፡ ለመስረቅ እና ሰዎችን አካል ተጎጂ ለማድረግ ተጠቅመውበታል። |
እና በስብዕና አንጻር ለፈፀሙት ወንጀል ተገቢውን ቅጣት ማግኘት አለባቸው። |
የቀድሞው የላይቤርያ ፕሬዚደንት ቻርልስ ቴይለር የተላለፈውን ብይን የተመድ እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች አሞገሱ። |
ይህ በዓለም አቀፍ የሕግና ፍትህ አሰራር ላይ ያላጥርጥር ታሪካዊ ሂደት መሆኑንም ፒላይ አክለው አስረድተዋል። |
ዓለም አቀፉ የወንጀል መርማሪ ሕግ ምን ያህል መጠናከሩን፡ ማለትም፡ ከፍተኛ ባለሥልጣናትን ሳይቀር በኃላፊነት ከመጠየቅ ወደኋላ እንደማይል አሳይቶዋል። |
በጣም በከፍተኛ ሥልጣን ላይ ያሉና የነበሩ ሁሉ በዓለም አቀፉ ሕግ ፊት ተጠያቂ ናቸው። |
Subsets and Splits
No community queries yet
The top public SQL queries from the community will appear here once available.